ታሪክን የኋሊት !
- eyobabyssinia
- Dec 6, 2025
- 1 min read

ታሪክን የኋሊት !
-------
#ኢትዮጵያ ከጥቂትቹ የጥቁር ሀገር ተሳታፊዎች አንዷ በሆነችበት የተመድ መስራች ጉባኤ የኢትዮጵያ ልዑካን በቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው እየተመራ በሳንፍራንሲስኮ እየመከረ ይገኛል-1937 ዓ.ም
➦የልዑካኑ አባላት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ነበሩ።
◈ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው፤ጠቅላይ ሚኒስትር እና የልዑካኑ መሪ፤
◈ፀሃፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ፤የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር፤
◈ዶክተር አምባዬ ወልደማርያም፤የፍትህ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር
◈ብላታ ኤፍሬም ተወልደመድህን፤በአሜሪካ የኢትዮጵያ ሚኒስትር/ጉዳይ ፈፃሚ፤ከቻርተሩ ፈራሚዎች አንዱ፤
◈አቶ አማኑኤል አብርሃም፤የትምህርት ሚኒስትር ዳይሬክተር ጀነራል፤
◈አቶ ምናሴ ለማ፤የፋይናስ ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀነራል
◈አቶ ጴጥሮስ ሣህሉ፤የልዑካኑ አባል
ኢትዮ ሰገነት ሚዲያ !


Comments